Publisher's Synopsis
ይህ አማርኛን በዘዴ የተሰኘው የአማርኛ መማሪያ መፅሐፍ በፋሬስ አካዳሚ ወስጥ ለማስተማሪያነት የተዛጋጀ ነው። ሆኖም ግን በዚህ አካዳሚ ውስጥ ተሳታፊ ለማይሆኑም ተማሪዎች በወላጆቻቸው አጋዥነት የአማርኛን ፊደላት መማር በሚችሉበት ሁኔታ የተዘጋጀ ነው። በየትኛውም ሃገር ውስጥ የሚኖሩ የዲያስፖራ ልጆችን የአማርኛ ቋንቋን ለማስተማር ይጠቅማል። በዚህ የደረጃ-አንድ መማሪያ መፅሐፍ ላይ ተማሪዎች ፊደላትን ለይተው እንዲያውቁና ፊደላትን ማንበብ እንዲሁም መፃፍ አንዲችሉ ይረዳቸው ዘንድ በአቅማቸው ተመጣጥኖ ተዘጋጅቷል ስለሆነም በደረጃ አንድ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉ ተማሪዎች ከዚህ በመቀጠል ከተዘረዘሩት ነጥቦች መሃል አንዱን ወይንም ሁሉንም ሊያሟሉ ይገባል ፦ - እድሜያቸው ከ 4 እስከ 6 የሆኑ ተማሪዎች መሆን ይኖርባቸዋል - የእንግሊዘኛን ቋንቋ በትንሽም ደረጃ ቢሆን መስማትና የተወሰኑ ቃላትን መናገር የሚችሉ - የእንግሊዝኛ ፊደላትን በደንብ ማንበብ የሚችሉ